Passport Services

አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች

  1. ኢትዮጵያ የተወለደ ግለሰብ ኢትዮጵያዊነቱን ለማጣራት የቀበሌ መታወቂያ፣ የትምህርት ማስረጃ ወይም ተያያዥ ሰነዶች ይዞ በመምጣት ሰነድ አልባ ቅፅ መሙላት፣          
  2. ጂቡቲ ለተወለደ ግለሰብ የቤተሰብ ማለት የእናትና አባት ወይም የአንዳቸውን ፓስፖርት ቅጅ ማቅረብ፣
  3. የልደት ሰርቲፊኬት ዋናውንና ቅጅ ማቅረብ፣      
  4. መነሻ ግድግዳቸው ነጭ የሆነ ሶስት ጉርድ 3X4 ፎቶግራፍ፣
  5. በኤምባሲው የጣት አሻራ መስጠት፣  

የፓስፖርት ዕድሳት ለማድረግ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች

  1. በእጅ ላይ ያለውን ፓስፖርት ዋናውንና አንድ ቅጅ ማቅረብ፣
  2. ከ6 ወር ወዲህ የተነሱ መነሻ ግድግዳቸው ነጭ የሆኑ ሶስት ባለ 3X4 ፎቶግራፍ፣
  3. 10,800 /አሥር ሺህ ስምንት መቶ የጂቡቲ ፍራንክ/ ክፍያ መፈፀም፣     

የጠፋ ፓስፖርት ምትክ ለማግኘት መሟላታ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች

  1. የነባሩ ፓስፖርት ቁጥር ወይም የፓስፖርት ቅጅ ማቅረብ፣
  2. ከጅቡቲ ፖሊስ ስለ መጥፋቱ ማስረጃ ማቅረብ፣           
  3. 16,200 /አሥር ስድስት ሺህ ሁለት መቶ የጂቡቲ ፍራንክ/ ክፍያ መፈፀም፣   

አዲስ ፓስፖርት ለማግኘት የሚያመለክቱ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያን ማሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች

  1. ኢትዮጵያ የተወለደ ግለሰብ ኢትዮጵያዊነቱን ለማጣራት የቀበሌ መታወቂያ፣ የትምህርት ማስረጃ፣ የልደት ወረቀት፣
    የመንጃ ፈቃድ ወይም ተያያዥ ሰነዶች ይዞ ወደ ኤምባሲው በመምጣት ሰነድ አልባ ቅፅ መሙላት፣
  2. ጂቡቲ ለተወለደ ግለሰብ የቤተሰብ ማለት የእናትና አባት ወይም የአንዳቸውን ፓስፖርት ቅጅ ማቅረብ፣ ጅቡቲ የተወለደ መሆኑን የሚያሳይ የልደት ሰርቲፊኬት ዋናውንና ቅጅ ማቅረብ፣
  3. መነሻ ግድግዳቸው ነጭ የሆነ ሶስት ጉርድ 3X4 ፎቶግራፍ፣
  4. በኤምባሲው በመገኘት አሻራ መስጠት፣

Loading

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X